ዜና
ትምህርት ቤቶችና አካባቢ የትምህርት አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከል በተዘጋጀው ረቂቅ ደንብ ላይ አግባብነት ካላቸው ሴክተር መሥሪያ ቤቶችና ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሂዷል።
የውይይት መድረኩን የከፈቱት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ የትምህርት አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከል የተዘጋጀው ረቂቅ ደንቡ ሰላማዊ መማር ማስተማርን በማስፈን ለተማሪዎች ውጤትና ሥነ-ምግባር መሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።
የመማር ማስተማር ሂደትን የሚያውኩ ጉዳዮች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ በመምጣታቸው ይህንን ለማስተካከል ረቂቅ ደንቡ መዘጋጀቱን ጠቅሰው ሁለንተናዊ ስብዕናው የተሟላ ዜጋ ማፍራት የደንቡ ዓላማ መሆኑን ተናግረዋል።
አክለውም ለተግባራዊነቱ ከሚመለከታቸው ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶና ተናቦ መሥራት እንደሚጠበቅ ሚኒስትር ደኤታዋ አሳስበዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የማህበራዊ ሳይንስ ትምህርቶች ሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ እቶ ኡመር ኢማም በበኩላቸው ረቂቅ ደንቡን ለማዳበር በርካታ የውይይት መድረኮች ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተካሄዱ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በየመድረኮቹ የሚነሱ ሀሳቦች በግብዓትነት ተወስደው ከተካተቱበት በኋላ ረቂቅ ደንቡ ሲጽድቅ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ተግባራዊ ይደረጋልም ነው ያሉት።
የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ባለፈው ዓመት የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ መውጣቱንና ይህም ደንብ አዋጁን ለማስፈጸም እየወጡ ካሉ የህግ ማዕቀፎች መካከል አንዱ መሆኑንም በመድረኩ ተጠቅሷል።
ትምህርት ቤቶችና አካባቢ የትምህርት አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከል በተዘጋጀው ረቂቅ ደንብ ላይ አግባብነት ካላቸው ሴክተር መሥሪያ ቤቶችና ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሂዷል።
የውይይት መድረኩን የከፈቱት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ የትምህርት አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከል የተዘጋጀው ረቂቅ ደንቡ ሰላማዊ መማር ማስተማርን በማስፈን ለተማሪዎች ውጤትና ሥነ-ምግባር መሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።
የመማር ማስተማር ሂደትን የሚያውኩ ጉዳዮች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ በመምጣታቸው ይህንን ለማስተካከል ረቂቅ ደንቡ መዘጋጀቱን ጠቅሰው ሁለንተናዊ ስብዕናው የተሟላ ዜጋ ማፍራት የደንቡ ዓላማ መሆኑን ተናግረዋል።
አክለውም ለተግባራዊነቱ ከሚመለከታቸው ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶና ተናቦ መሥራት እንደሚጠበቅ ሚኒስትር ደኤታዋ አሳስበዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የማህበራዊ ሳይንስ ትምህርቶች ሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ እቶ ኡመር ኢማም በበኩላቸው ረቂቅ ደንቡን ለማዳበር በርካታ የውይይት መድረኮች ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተካሄዱ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በየመድረኮቹ የሚነሱ ሀሳቦች በግብዓትነት ተወስደው ከተካተቱበት በኋላ ረቂቅ ደንቡ ሲጽድቅ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ተግባራዊ ይደረጋልም ነው ያሉት።
የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ባለፈው ዓመት የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ መውጣቱንና ይህም ደንብ አዋጁን ለማስፈጸም እየወጡ ካሉ የህግ ማዕቀፎች መካከል አንዱ መሆኑንም በመድረኩ ተጠቅሷል።
Oct 24, 2025
177
የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ይዘቶች ይፋ ሆኑ፡፡
ተማሪዎች፣ የተማሪ ቤተሰቦች፣ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ለፈተና ዝግጅት በሚያደርጉበት ወቅት ፈተና የሚሸፍናቸውን የይዘት አካባቢዎች ማወቅ አስፈላጊ መሆኑ ይታመናል። በመሆኑም የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ከፍል ፈተና ዝግጅትና አስተዳደር የሚከተሉትን ያካትታል፡፡
1. የትምህርት ዓይነቶችን በተመለከተ ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ኬሚስትሪ፣ ፊዝክስና ባዮሎጂ እንዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊና ኢኮኖሚክስ ናቸው።
2. ፈተናው ከ9ኛ እስከ 12ኛ ከፍል ደረጃዎችን እና በተማሪው መጽሐፍ ላይ ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች ይሸፍናል፡፡
3. ከ10ኛ – 12ኛ ክፍል ሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ፈተና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት እየተዘጋጀ ያለ ሲሆን የ9ኛ ክፍል ደግሞ የሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ፈተናዎች ከቀድሞውና ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘቶችን ብቻ አካቶ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡
4. ፈተናው ማንኛውም ተፈታኝ ተማሪ ከተማረው ሥርዓተ ትምህርትና ከተማሪው መጽሐፍ ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚዘጋጅ ይሆናል፤
5. የፈተናው አስተዳደር በበይነ መረብና በወረቀት ጎን ለጎን የሚሰጥ ሲሆን አብዛኛው ተፈታኝ በበይነ መረብ እንዲፈተን እየተሠራ ያለ በመሆኑ ተፈታኞች እራሳቸውን በበይነ መረብ ለመፈተን ሊያዘጋጁ እንደሚገባ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል፡፡
ተማሪዎች፣ የተማሪ ቤተሰቦች፣ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ለፈተና ዝግጅት በሚያደርጉበት ወቅት ፈተና የሚሸፍናቸውን የይዘት አካባቢዎች ማወቅ አስፈላጊ መሆኑ ይታመናል። በመሆኑም የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ከፍል ፈተና ዝግጅትና አስተዳደር የሚከተሉትን ያካትታል፡፡
1. የትምህርት ዓይነቶችን በተመለከተ ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ኬሚስትሪ፣ ፊዝክስና ባዮሎጂ እንዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊና ኢኮኖሚክስ ናቸው።
2. ፈተናው ከ9ኛ እስከ 12ኛ ከፍል ደረጃዎችን እና በተማሪው መጽሐፍ ላይ ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች ይሸፍናል፡፡
3. ከ10ኛ – 12ኛ ክፍል ሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ፈተና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት እየተዘጋጀ ያለ ሲሆን የ9ኛ ክፍል ደግሞ የሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ፈተናዎች ከቀድሞውና ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘቶችን ብቻ አካቶ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡
4. ፈተናው ማንኛውም ተፈታኝ ተማሪ ከተማረው ሥርዓተ ትምህርትና ከተማሪው መጽሐፍ ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚዘጋጅ ይሆናል፤
5. የፈተናው አስተዳደር በበይነ መረብና በወረቀት ጎን ለጎን የሚሰጥ ሲሆን አብዛኛው ተፈታኝ በበይነ መረብ እንዲፈተን እየተሠራ ያለ በመሆኑ ተፈታኞች እራሳቸውን በበይነ መረብ ለመፈተን ሊያዘጋጁ እንደሚገባ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል፡፡
Oct 23, 2025
229
የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር ለፌደራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመምህርነት ለተመዘገባችሁ ተወዳዳሪዎች በሙሉ፤
የጽሁፍ ፈተና በተመረጡ 18 ዩኒቨርስቲዎች ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል፡፡ ስለሆነም ሁሉም ተፈታኝ መምህራን ጥቅምት 17/2018ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ከታች ከተዘረዘሩት የዩኒቨርስቲ አማራጮች በሚቀርባችሁ ዩኒቨርስቲ በመገኘት መፈተን የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ከዚህ በፊት ከነበረው ስም ዝርዝር በተጨማሪ እንደ አዲስ የተካተታችሁ ስላላችሁ ስማችሁን በድጋሚ በ(https://sbs.moe.gov.et/career/check-status) በመግባት ማረጋገጥ የምትችሉ መሆኑንን እየገለፅን በተጨማሪም የሚቀርባችሁን የፈተና ማዕከል (ዩኒቨርሲቲ) መርጣችሁ እንድታስገቡ እናሳውቃለን፡፡
ማሳሰቢያ፤ ማንኛውም መምህር ለፈተና ወደ ዩኒቨርስቲ ሲመጣ ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ ይዞ መቅረበ ይኖርበታል።
የፈተና መስጫ ማዕከላት (Exam center)
1. ወሎ ዩኒቨርስቲ
2. ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
3. ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
4. ጅማ ዩኒቨርሲቲ
5. አርሲ ዩኒቨርሲቲ
6. ወለጋ ዩኒቨርሲቲ
7. ጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ
8. ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ
9. ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ
10. አሶሳ ዩኒቨርሲቲ
11. ዋቻም ዩኒቨርሲቲ
12. ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
13. አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
14. ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ
15. መቀሌ ዩኒቨርሲቲ
16. አክሱም ዩኒቨርሲቲ
17. ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ
18. ደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ
የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር ለፌደራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመምህርነት ለተመዘገባችሁ ተወዳዳሪዎች በሙሉ፤
የጽሁፍ ፈተና በተመረጡ 18 ዩኒቨርስቲዎች ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል፡፡ ስለሆነም ሁሉም ተፈታኝ መምህራን ጥቅምት 17/2018ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ከታች ከተዘረዘሩት የዩኒቨርስቲ አማራጮች በሚቀርባችሁ ዩኒቨርስቲ በመገኘት መፈተን የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ከዚህ በፊት ከነበረው ስም ዝርዝር በተጨማሪ እንደ አዲስ የተካተታችሁ ስላላችሁ ስማችሁን በድጋሚ በ(https://sbs.moe.gov.et/career/check-status) በመግባት ማረጋገጥ የምትችሉ መሆኑንን እየገለፅን በተጨማሪም የሚቀርባችሁን የፈተና ማዕከል (ዩኒቨርሲቲ) መርጣችሁ እንድታስገቡ እናሳውቃለን፡፡
ማሳሰቢያ፤ ማንኛውም መምህር ለፈተና ወደ ዩኒቨርስቲ ሲመጣ ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ ይዞ መቅረበ ይኖርበታል።
የፈተና መስጫ ማዕከላት (Exam center)
1. ወሎ ዩኒቨርስቲ
2. ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
3. ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
4. ጅማ ዩኒቨርሲቲ
5. አርሲ ዩኒቨርሲቲ
6. ወለጋ ዩኒቨርሲቲ
7. ጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ
8. ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ
9. ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ
10. አሶሳ ዩኒቨርሲቲ
11. ዋቻም ዩኒቨርሲቲ
12. ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
13. አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
14. ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ
15. መቀሌ ዩኒቨርሲቲ
16. አክሱም ዩኒቨርሲቲ
17. ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ
18. ደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ
Oct 23, 2025
175
ውይይቱ በትምህርቱ ዘርፉ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችና የቅሬታ አፈታት አሰራር ስርዓቶች ላይ ያተኮረ ሲሆን የተዘረጉ የአደረጃጀትና የአሠራር ስርዓቶች በትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት የስራ ሀላፊዎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የቀረበውን የውይይት መነሻ ሀሳብ በመንተራስ ሀሳባቸውን ያጋሩት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በየደረጃው ባለ መዋቅር የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችና ቅሬታዎችን ለመፍታት የተለያዩ አደረጃጀቶችና የአሰራር ስርዓቶችን ወደ ተግባር በማስገባት ተገልጋዬችን ከዕንግልት፣ ከተጨማሪ የጊዜና ገንዘብ ወጪ ማዳን መቻሉን ገልጸዋል።
አሳታፊነት ከማጠናከርና ከማረጋገጥ አኳያ ከዘርፉ ተዋንያን ጋር በጋራ የማቀድ፣ የመከታተል፣ የመገምገምና ግብረ መልስ የመስጠት ተግባራት በመከናወን ላይ መሆናቸውን ክብርት ወ/ሮ አየለች አያይዘው ገልጸዋል ።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚስተዋሉና የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችና የቅሬታ አፈታት ስርዓቶችን ለማሻሻል በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎችን አብራርተዋል።
በተማሪ ቅበላ ፣ በፈተና አስተዳደር፣በመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ የሚያጋጥሙ የመልካም አሰተዳደር ጥያቄዎችና ቅሬታዎችን ቀድሞ የማወቅና የመከላከል ተግባራት ላይ በትኩረት እየተሠራ መሆኑንም አያይዘው ገልጸዋል።
በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት የመልካም አስተዳደር ጉዳዬችና የቅሬታ አፈታት መሪ ስራ አስፈጻሚ ፍቅሩ ወርቁ በበኩላቸው በትምህርት ዘርፉ የሚስተዋሉና የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችና ቅሬታዎች ለመከላከልና ለመፍታት በመከናወን ላይ ያሉ የአደረጃጀትና የአሠራር ስርዓቶች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።
የስራ ሀላፊው አያይዘውም በትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በኩል የተዘረጉት የመልካም አስተዳደርና የቅሬታ አፈታት አደረጃደትና አሠራር ስርዓቶች ለሌሎች ተቋማት ተሞክሮና ልምድ የሚቀሠምባቸው መሆኑን አመላክተዋል።
ውይይቱ በትምህርቱ ዘርፉ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችና የቅሬታ አፈታት አሰራር ስርዓቶች ላይ ያተኮረ ሲሆን የተዘረጉ የአደረጃጀትና የአሠራር ስርዓቶች በትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት የስራ ሀላፊዎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የቀረበውን የውይይት መነሻ ሀሳብ በመንተራስ ሀሳባቸውን ያጋሩት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በየደረጃው ባለ መዋቅር የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችና ቅሬታዎችን ለመፍታት የተለያዩ አደረጃጀቶችና የአሰራር ስርዓቶችን ወደ ተግባር በማስገባት ተገልጋዬችን ከዕንግልት፣ ከተጨማሪ የጊዜና ገንዘብ ወጪ ማዳን መቻሉን ገልጸዋል።
አሳታፊነት ከማጠናከርና ከማረጋገጥ አኳያ ከዘርፉ ተዋንያን ጋር በጋራ የማቀድ፣ የመከታተል፣ የመገምገምና ግብረ መልስ የመስጠት ተግባራት በመከናወን ላይ መሆናቸውን ክብርት ወ/ሮ አየለች አያይዘው ገልጸዋል ።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚስተዋሉና የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችና የቅሬታ አፈታት ስርዓቶችን ለማሻሻል በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎችን አብራርተዋል።
በተማሪ ቅበላ ፣ በፈተና አስተዳደር፣በመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ የሚያጋጥሙ የመልካም አሰተዳደር ጥያቄዎችና ቅሬታዎችን ቀድሞ የማወቅና የመከላከል ተግባራት ላይ በትኩረት እየተሠራ መሆኑንም አያይዘው ገልጸዋል።
በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት የመልካም አስተዳደር ጉዳዬችና የቅሬታ አፈታት መሪ ስራ አስፈጻሚ ፍቅሩ ወርቁ በበኩላቸው በትምህርት ዘርፉ የሚስተዋሉና የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችና ቅሬታዎች ለመከላከልና ለመፍታት በመከናወን ላይ ያሉ የአደረጃጀትና የአሠራር ስርዓቶች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።
የስራ ሀላፊው አያይዘውም በትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በኩል የተዘረጉት የመልካም አስተዳደርና የቅሬታ አፈታት አደረጃደትና አሠራር ስርዓቶች ለሌሎች ተቋማት ተሞክሮና ልምድ የሚቀሠምባቸው መሆኑን አመላክተዋል።
Oct 22, 2025
162
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ከቻይናዋ ሻንዢ ግዛት ምክትል ገዢ ዋንግ ዢአዎ የተመራ ልዑካን ቡድን ባነጋገሩበት ወቅት እንደገለጹት በኢትዮጵያና በቻይና መካከል ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ የትብብር ግንኙነት መኖሩን ጠቅሰዋል፡፡
በሁለቱ አገራት መካከል ያለው የትብብር ግንኙነት በአሁኑ ጊዜ ወደ ስትራጂካው አጋርነት መሸጋገሩንም ክቡር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል፡፡
የቻይና የስልጣኔ ማዕከል የሆነችው የሻንዢ ግዛት ከኢትዮጵያ ጋር በባቡር ፣ በቴክኒክና ሙያ እና በሌሎችም መስኮች የትብብር ግንኙነት እንዳላትና ትምህርት ሚኒስቴር ከግዛቲቱ ጋር ያለውን ትብብር በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍም ማጠናከር እንደሚፈልግ ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በርካታ ዩኒቨርስቲዎች መገንባታቸውንና በአሁኑ ወቅት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ጥራት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ግዛቲቱ በሳይንስ ፣ በቴክኖሎጂና በሌሎችም መስኮች ያላትን ልምድና ተሞክሮ ለኢትዮጵያ ጠቃሚ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
በግብርና ምርምር ፣ በኢኖቬሽን፣ በትምህርትና በአቅም ግንባታ መስኮች በትብብር በመሰራት ግዛቲቱ ከጅማ ዩኒቨርስቲ ጋር የተፈራረመችው የመግባቢየ ስምምነት በአርአያነት የሚታይ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
ቻይናዋ ሻንዢ ግዛት ምክትል ገዢ ሚስተር ዋንግ ዚአዎ በበኩላቸው ኢትዮጵያና ቻይና ዘርፈ ብዙ ስትራቴጂካዊ አጋሮችና ወዳጆች መሆናቸውን ገልጸው የሁለቱ አገራት ግንኙነት በቻይና አፍሪካ ግንኙነትም በግንባር ቀደምነት የሚታይና በማደግ ላይ ላሉ አገራትም በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
በሻንዢ ግዛት በኢትዮጵያ በትምህርት መስኩ በተለይም በነጻ የትምህርት እድል ፣ በምርምር፣ በኢንጂነሪንግ ፣ በእርሻ ፣ በህብረተሰብ ጤና እና በሌሎችም የትብብርመስኮች ያለውን ግንኙነት ማጠናከርና ማስቀጠል እንደምትፈልግም አስታውቀዋል።
በዚህ ዓመትም በግዛቲቱ ውስጥ በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች 5 ነጻ የትምህርት እድል ለመስተት ዝግጁ መሆኗንም የቻይናዋ ሻንዢ ግዛት ምክትል ገዢ ሚስተር ዋንግ ዚአዎ ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም የጅማ ዩኒቨርስቲ ፕሩዚዳንት ጀማል አባ ፊጣ (ዶ/ር) እና በቻይና የያንግሊንግ አግሪካልቸራል ሃይ-ቴክ ኢንደስትሪያል ዲሞንስትሬሽን ዞን (Agricultural High-Tech Industrial Demonstration Zone, China) ምክትል ጸሀፊ ሚስተር ዋንግ ጁን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ከቻይናዋ ሻንዢ ግዛት ምክትል ገዢ ዋንግ ዢአዎ የተመራ ልዑካን ቡድን ባነጋገሩበት ወቅት እንደገለጹት በኢትዮጵያና በቻይና መካከል ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ የትብብር ግንኙነት መኖሩን ጠቅሰዋል፡፡
በሁለቱ አገራት መካከል ያለው የትብብር ግንኙነት በአሁኑ ጊዜ ወደ ስትራጂካው አጋርነት መሸጋገሩንም ክቡር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል፡፡
የቻይና የስልጣኔ ማዕከል የሆነችው የሻንዢ ግዛት ከኢትዮጵያ ጋር በባቡር ፣ በቴክኒክና ሙያ እና በሌሎችም መስኮች የትብብር ግንኙነት እንዳላትና ትምህርት ሚኒስቴር ከግዛቲቱ ጋር ያለውን ትብብር በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍም ማጠናከር እንደሚፈልግ ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በርካታ ዩኒቨርስቲዎች መገንባታቸውንና በአሁኑ ወቅት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ጥራት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ግዛቲቱ በሳይንስ ፣ በቴክኖሎጂና በሌሎችም መስኮች ያላትን ልምድና ተሞክሮ ለኢትዮጵያ ጠቃሚ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
በግብርና ምርምር ፣ በኢኖቬሽን፣ በትምህርትና በአቅም ግንባታ መስኮች በትብብር በመሰራት ግዛቲቱ ከጅማ ዩኒቨርስቲ ጋር የተፈራረመችው የመግባቢየ ስምምነት በአርአያነት የሚታይ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
ቻይናዋ ሻንዢ ግዛት ምክትል ገዢ ሚስተር ዋንግ ዚአዎ በበኩላቸው ኢትዮጵያና ቻይና ዘርፈ ብዙ ስትራቴጂካዊ አጋሮችና ወዳጆች መሆናቸውን ገልጸው የሁለቱ አገራት ግንኙነት በቻይና አፍሪካ ግንኙነትም በግንባር ቀደምነት የሚታይና በማደግ ላይ ላሉ አገራትም በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
በሻንዢ ግዛት በኢትዮጵያ በትምህርት መስኩ በተለይም በነጻ የትምህርት እድል ፣ በምርምር፣ በኢንጂነሪንግ ፣ በእርሻ ፣ በህብረተሰብ ጤና እና በሌሎችም የትብብርመስኮች ያለውን ግንኙነት ማጠናከርና ማስቀጠል እንደምትፈልግም አስታውቀዋል።
በዚህ ዓመትም በግዛቲቱ ውስጥ በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች 5 ነጻ የትምህርት እድል ለመስተት ዝግጁ መሆኗንም የቻይናዋ ሻንዢ ግዛት ምክትል ገዢ ሚስተር ዋንግ ዚአዎ ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም የጅማ ዩኒቨርስቲ ፕሩዚዳንት ጀማል አባ ፊጣ (ዶ/ር) እና በቻይና የያንግሊንግ አግሪካልቸራል ሃይ-ቴክ ኢንደስትሪያል ዲሞንስትሬሽን ዞን (Agricultural High-Tech Industrial Demonstration Zone, China) ምክትል ጸሀፊ ሚስተር ዋንግ ጁን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
Oct 21, 2025
104
የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች “ብሄራዊ ጥቅምና ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና” በሚል ርዕስ በተዘገጃ ሀገራዊ ሰነድ ላይ ውይይት አካሄዱ፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች “ብሄራዊ ጥቅምና ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና” በሚል ርዕስ በተዘጋጃ ሀገራዊ ሰነድ ላይ ውይይት አካሄደዋል፡፡
በተዘጋጀው ሀገራዊ ሰነድና ተዛማጅ ጉዳዬች ላይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌስር ብርሃኑ ነጋ ባጋሩት ሀሳብ እየተቀየረ ያለውን የዓለም ጂኦፓለቲክስ ቀድሞ በመረዳት የሀገራችንን ስትራቴጂያዊ አካሄድና ብሄራዊ ጥቅም ለማረጋገጥ የሚያስችል ዝግጁነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በአሁኑ ወቅት እንደ ሀገር ብሄራዊ ጥቅሞች ለማረጋገጥ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ልዩነቶቾን በማጉላት መደነቃቀፍን የሚፈጥሩ አጀንዳዎች፣አመለካከቶችና ሌሎች ፈተናዎችን በማስወገድ ሁሉም የድርሻውን መወጣት እንደሚገባው አስገንዝበዋል፡፡
ሀገር ያለ ብሔራዊ ጥቅም ልትቀጥል እንደማትችል አጽንኦት ሰጥተው የተናገሩት ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን በጥልቀት መረዳት እንደሚገባም አብራርተዋል።
አክለውም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ዋና ዋና ፈተናዎች ጂኦስትራቴጂያዊ ጉዳዮችና እና መልከዓ ምድራዊ የሆኑ ተግዳሮቶች እንደሆኑ አመላክተው እነዚህን ተግዳሮቶች ለመሻገር ዓለም አቀፋዊ ሕጎችን መሠረት በማድረግ ብሔራዊ ጥቅምን ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ የተፈጥሮ ሀብት፣ የህዝብ ብዛት፣ ጅኦፖለቲካዊ አቀማመጥ እና የተደራጀ ተቋማዊ አቅምን አስተሳስረን ተለዋዋጭ በሆነው የዓለማችን ሁኔታ ውስጥ ብሔራዊ ጥቅማችንን ለማስጠበቅ ተግቶ መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ያለህዝብ ተሳትፎ በመንግሥት ብቻ መሰልና ወሳኝ የሆኑ ብሄራዊ ጥቅሞችን ማስጠበቅም ይሁን ማሳካት የማይችል መሆኑን በመጥቀስ ህዝቡ ከማንነቱ፣ ከህልውናውና ከነገ ተስፋው ጋር የተሳሰረውን ብሔራዊ ጥቅም እንዲሁም ጆኦስትራቴጂካዊ ቁመና ጉዳይ ላይ በትኩረት ሊመለከተውና ሊሠራበት እንደሚገባም ገልጸዋል።
በቀረበው ሀገራዊ ሠነድ ላይ ከትምህርት ዘርፉ ሰራተኞች ምን ይጠበቃል በሚለው ጉዳይ ላይ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶች ቀርበው ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች “ብሄራዊ ጥቅምና ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና” በሚል ርዕስ በተዘጋጃ ሀገራዊ ሰነድ ላይ ውይይት አካሄደዋል፡፡
በተዘጋጀው ሀገራዊ ሰነድና ተዛማጅ ጉዳዬች ላይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌስር ብርሃኑ ነጋ ባጋሩት ሀሳብ እየተቀየረ ያለውን የዓለም ጂኦፓለቲክስ ቀድሞ በመረዳት የሀገራችንን ስትራቴጂያዊ አካሄድና ብሄራዊ ጥቅም ለማረጋገጥ የሚያስችል ዝግጁነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በአሁኑ ወቅት እንደ ሀገር ብሄራዊ ጥቅሞች ለማረጋገጥ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ልዩነቶቾን በማጉላት መደነቃቀፍን የሚፈጥሩ አጀንዳዎች፣አመለካከቶችና ሌሎች ፈተናዎችን በማስወገድ ሁሉም የድርሻውን መወጣት እንደሚገባው አስገንዝበዋል፡፡
ሀገር ያለ ብሔራዊ ጥቅም ልትቀጥል እንደማትችል አጽንኦት ሰጥተው የተናገሩት ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን በጥልቀት መረዳት እንደሚገባም አብራርተዋል።
አክለውም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ዋና ዋና ፈተናዎች ጂኦስትራቴጂያዊ ጉዳዮችና እና መልከዓ ምድራዊ የሆኑ ተግዳሮቶች እንደሆኑ አመላክተው እነዚህን ተግዳሮቶች ለመሻገር ዓለም አቀፋዊ ሕጎችን መሠረት በማድረግ ብሔራዊ ጥቅምን ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ የተፈጥሮ ሀብት፣ የህዝብ ብዛት፣ ጅኦፖለቲካዊ አቀማመጥ እና የተደራጀ ተቋማዊ አቅምን አስተሳስረን ተለዋዋጭ በሆነው የዓለማችን ሁኔታ ውስጥ ብሔራዊ ጥቅማችንን ለማስጠበቅ ተግቶ መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ያለህዝብ ተሳትፎ በመንግሥት ብቻ መሰልና ወሳኝ የሆኑ ብሄራዊ ጥቅሞችን ማስጠበቅም ይሁን ማሳካት የማይችል መሆኑን በመጥቀስ ህዝቡ ከማንነቱ፣ ከህልውናውና ከነገ ተስፋው ጋር የተሳሰረውን ብሔራዊ ጥቅም እንዲሁም ጆኦስትራቴጂካዊ ቁመና ጉዳይ ላይ በትኩረት ሊመለከተውና ሊሠራበት እንደሚገባም ገልጸዋል።
በቀረበው ሀገራዊ ሠነድ ላይ ከትምህርት ዘርፉ ሰራተኞች ምን ይጠበቃል በሚለው ጉዳይ ላይ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶች ቀርበው ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
Oct 20, 2025
127
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጲያ UNFPA ተወካይ ጋር ተወያዩ።
የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጲያ የUNFPA ተወካይ Mr. Sk Kouameን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ በኢትዮጲያ UNFPA ተወካይ የሆኑት Mr. Sk Kouame UNFPA በሴቶች ትምህርት በተለይም ለሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ግብዓቶችን በማቅረብ እየሰራ መሆኑን በመጥቀስ በቀጣይም ይህንን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ለክቡር ሚኒስትሩ አብራርተውላቸዋል።
UNFPA ከትምህርት ሚኒስቴር እና ከሌሎች ጋር በመተባበር የሴቶችን የትምህርት ሁኔታ በማመቻቸት ረገድ የበለጠ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንደሚፈልጉም ገልጸውላቸዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ በበኩላቸው UNFPA ውስን በሆነ መልኩ ለሴት ተማሪዎች ሲያደርግ የነበረውን ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።
አክለውም በቀጣይ ከእንዲህ ዓይነት ውስን ድጋፎች ተላቆ በራስ አቅም የሴቶችን ንጽህና መጠበቂያ በማምረት ለኢትዮጵያም ብሎም ለአፍሪካ የሚጠቅም ሥራ መስራት እንደሚገባ ለካንትሪ ዳይሬክተሩ አብራርተውላቸዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጲያ የUNFPA ተወካይ Mr. Sk Kouameን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ በኢትዮጲያ UNFPA ተወካይ የሆኑት Mr. Sk Kouame UNFPA በሴቶች ትምህርት በተለይም ለሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ግብዓቶችን በማቅረብ እየሰራ መሆኑን በመጥቀስ በቀጣይም ይህንን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ለክቡር ሚኒስትሩ አብራርተውላቸዋል።
UNFPA ከትምህርት ሚኒስቴር እና ከሌሎች ጋር በመተባበር የሴቶችን የትምህርት ሁኔታ በማመቻቸት ረገድ የበለጠ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንደሚፈልጉም ገልጸውላቸዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ በበኩላቸው UNFPA ውስን በሆነ መልኩ ለሴት ተማሪዎች ሲያደርግ የነበረውን ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።
አክለውም በቀጣይ ከእንዲህ ዓይነት ውስን ድጋፎች ተላቆ በራስ አቅም የሴቶችን ንጽህና መጠበቂያ በማምረት ለኢትዮጵያም ብሎም ለአፍሪካ የሚጠቅም ሥራ መስራት እንደሚገባ ለካንትሪ ዳይሬክተሩ አብራርተውላቸዋል።
Oct 20, 2025
107
የማጠናከሪያ ትምህር በዕቅድና በትኩረት እንዲመራ ትምህርት ሚኒስቴር አሳሰበ
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት አየለች እሸቴ ከክልልና ከከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በበይነ መረብ ውይይት ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት በአጠቃላይ ከ9ኛ ክፍል ጀምሮ በተለይም ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርትን በዕቅድና በትኩረት እንዲሰራ አሳስበዋል።
የተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ መምህራን፣ የትምህርት ቤት አመራሮች፣ ወላጆች እንዲሁም የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ተማሪዎች ጊዚያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ ከወዲሁ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸው ክብርት ወ/ሮ አየለች አስገንዝበዋል።
የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች በበኩላቸው የማጠናከሪያ ትምህርት ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል ጠቀሜታው የላቀ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።
የትምህርት ፕሮግራሞች ጥራትና መሻሻል መሪ ስራ አስፈጻሚ ዩሀንስ ወጋሶ(ዶ/ር) የማጠናከሪያ ትምህርትን በተመለከተ መነሻ ስትራቴጂ እቅድ ያቀረቡ ሲሆን የተያዘው ግብ እንዲሳካ ከወዲሁ የዕቅድ ክትትልና ድጋፍ ሥራዎች ሊጠናከሩ ይገባል ብለዋል።
በበይነ-መረብ በተደረገው በዚሁ ውይይት ላይ የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችን ፣ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) እና ሌሎችም የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት አየለች እሸቴ ከክልልና ከከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በበይነ መረብ ውይይት ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት በአጠቃላይ ከ9ኛ ክፍል ጀምሮ በተለይም ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርትን በዕቅድና በትኩረት እንዲሰራ አሳስበዋል።
የተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ መምህራን፣ የትምህርት ቤት አመራሮች፣ ወላጆች እንዲሁም የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ተማሪዎች ጊዚያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ ከወዲሁ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸው ክብርት ወ/ሮ አየለች አስገንዝበዋል።
የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች በበኩላቸው የማጠናከሪያ ትምህርት ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል ጠቀሜታው የላቀ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።
የትምህርት ፕሮግራሞች ጥራትና መሻሻል መሪ ስራ አስፈጻሚ ዩሀንስ ወጋሶ(ዶ/ር) የማጠናከሪያ ትምህርትን በተመለከተ መነሻ ስትራቴጂ እቅድ ያቀረቡ ሲሆን የተያዘው ግብ እንዲሳካ ከወዲሁ የዕቅድ ክትትልና ድጋፍ ሥራዎች ሊጠናከሩ ይገባል ብለዋል።
በበይነ-መረብ በተደረገው በዚሁ ውይይት ላይ የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችን ፣ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) እና ሌሎችም የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
Oct 19, 2025
88
በመርሀ-ግብሩ ላይ የተገኙት ትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በሀረሪ ክልል በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የተመዘገበው 22 በመቶ ውጤት አበረታች መሆኑን ጠቁመው ክልሉ ለትምህርቱ ዘርፍ የሰጠውን ትኩረት ማሳያ ነው ብለዋል።
እንደ ሀገር በትምህርት ዘርፉ የሰራና የለፋ ብቻ ውጤት የሚያገኝበት ሥርዓት እየተዘረጋ መጥቷል ያሉት ሚኒስትሩ ዛሬ የተሸለማችሁ በአቋራጭ ሳይሆን በስራና በድካም ያገኛችሁት ውጤት በመሆኑ ልትኮሩ ይገባችኋል ብለዋል።
በቀጣዩ የ2018 የትምህርት ዘመንም የ12 ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና በክልሉ ሙሉ በመሉ ከወረቀት ነፃ በሆነ መልኩ በኦላይን ለመስጠት ከክልሉ አመራር ጋር መግባባት መደረሱንም ሚኒስትሩ ገልፀዋል።
በመሆኑም በክልሉ አሁን በተገኘው ውጤት መዘናጋት ሳይኖር የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።
ሚኒስትሩ አክለውም ይሄ ትውልድ የሥራ ትውልድ፣ በራሱ የሚኮራ ትውልድ እንዲሆን እንደ ሀገር የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል።
በዕውቅናና ሽልማት መርሀ-ግብሩ ላይ የትምህርት ሚኒስቴርና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በመርሀ-ግብሩ ላይ የተገኙት ትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በሀረሪ ክልል በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የተመዘገበው 22 በመቶ ውጤት አበረታች መሆኑን ጠቁመው ክልሉ ለትምህርቱ ዘርፍ የሰጠውን ትኩረት ማሳያ ነው ብለዋል።
እንደ ሀገር በትምህርት ዘርፉ የሰራና የለፋ ብቻ ውጤት የሚያገኝበት ሥርዓት እየተዘረጋ መጥቷል ያሉት ሚኒስትሩ ዛሬ የተሸለማችሁ በአቋራጭ ሳይሆን በስራና በድካም ያገኛችሁት ውጤት በመሆኑ ልትኮሩ ይገባችኋል ብለዋል።
በቀጣዩ የ2018 የትምህርት ዘመንም የ12 ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና በክልሉ ሙሉ በመሉ ከወረቀት ነፃ በሆነ መልኩ በኦላይን ለመስጠት ከክልሉ አመራር ጋር መግባባት መደረሱንም ሚኒስትሩ ገልፀዋል።
በመሆኑም በክልሉ አሁን በተገኘው ውጤት መዘናጋት ሳይኖር የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።
ሚኒስትሩ አክለውም ይሄ ትውልድ የሥራ ትውልድ፣ በራሱ የሚኮራ ትውልድ እንዲሆን እንደ ሀገር የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል።
በዕውቅናና ሽልማት መርሀ-ግብሩ ላይ የትምህርት ሚኒስቴርና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
Oct 19, 2025
86
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በእንግሊዝ መንግስት የFCDO የኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር ሆነው የተመደቡትን Amanda McLoughlin በጽ/ቤታቸው ተቀብለው በኢትዮጵያ በሚሰሩ የሪፎርም ስራዎች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።
በዚሁ ወቅት የትምህርት ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ በርካታ የሪፎርም ተግባራትን እየተገበረች መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም የተጀመሩ የሪፎርም ተግባራት የበለጠ እንዲሳኩ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የቅድሚያ ትኩረት በሰጣቸው ጉዳዮች ላይ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ጠቅሰዋል።
በመሆኑም Education Transformation Operation for Learning (ETOL) ፕሮጀክት የሚደረገው የገንዘብ ድጋፍ እንዲፈጥን ጠይቀው፤ ለትምህርት ጥራት መውደቅ አንዱ ምክንያት የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ማነስ በመሆኑ በዚህ ረገድ ድጋፉ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አሳስበዋል።
አዲሷ የ FCDO የኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር Amanda McLoughlin በበኩላቸው በትምህርቱ ዘርፍ ለተጀመሩ የሪፎርም ተግባራት አድናቆት እንዳላቸው ገልጸው፣ FCDO ለኢትዮጵያ የሚያደርገው ቴክኒካል ድጋፍ ይቀጥላል ብለዋል።
በተለይም የእንግሊዝ መንግስት ድጋፍ ለማድረግ ከለያቸው አስር የአፍሪካ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ ግንባር ቀደም መሆኗን ጠቅሰው በ ETOL ፕሮጅክት እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ ማሻሻያ መርሃ ግብር የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ዋና ዳይሬክተሯ ተናግረዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በእንግሊዝ መንግስት የFCDO የኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር ሆነው የተመደቡትን Amanda McLoughlin በጽ/ቤታቸው ተቀብለው በኢትዮጵያ በሚሰሩ የሪፎርም ስራዎች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።
በዚሁ ወቅት የትምህርት ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ በርካታ የሪፎርም ተግባራትን እየተገበረች መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም የተጀመሩ የሪፎርም ተግባራት የበለጠ እንዲሳኩ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የቅድሚያ ትኩረት በሰጣቸው ጉዳዮች ላይ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ጠቅሰዋል።
በመሆኑም Education Transformation Operation for Learning (ETOL) ፕሮጀክት የሚደረገው የገንዘብ ድጋፍ እንዲፈጥን ጠይቀው፤ ለትምህርት ጥራት መውደቅ አንዱ ምክንያት የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ማነስ በመሆኑ በዚህ ረገድ ድጋፉ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አሳስበዋል።
አዲሷ የ FCDO የኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር Amanda McLoughlin በበኩላቸው በትምህርቱ ዘርፍ ለተጀመሩ የሪፎርም ተግባራት አድናቆት እንዳላቸው ገልጸው፣ FCDO ለኢትዮጵያ የሚያደርገው ቴክኒካል ድጋፍ ይቀጥላል ብለዋል።
በተለይም የእንግሊዝ መንግስት ድጋፍ ለማድረግ ከለያቸው አስር የአፍሪካ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ ግንባር ቀደም መሆኗን ጠቅሰው በ ETOL ፕሮጅክት እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ ማሻሻያ መርሃ ግብር የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ዋና ዳይሬክተሯ ተናግረዋል።
Oct 17, 2025
86
የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ከአለም የምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ ዋና ምክትል ኃላፊ ጋር ተወያዩ፤
የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታዋ የአለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ ምክትል ኃላፊ ሙቲንታ ሀምባይን (ዶ/ር) በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ሁለቱ አካላት በቀጣይ የኢትዮጵያ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብርን ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል።
በዚሁ ጊዜ ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ የኢትዮጵያ መንግሥት ለትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ለመርሃ-ግብሩ የሚመድቡት በጀት አየጨመረ መምጣቱንና ህብረተሰቡም ለመርሃ-ግብሩ ውጤታማነት የሚያደርገው ተሳትፎ በየጊዜው እያደገ የመጣ መሆኑን አንስተዋል፡፡
የአለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ሙቲንታ በበኩላቸው የኢትዮጵያ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር በአፍሪካ ትልቁና ቀዳሚ መሆኑን ጠቅሰው በቅርቡ በተካሄደው አለም አቀፍ የትምህርት ቤት ምገባ ጥምረት ስብሰባ ላይ እውቅና የተሰጠውና በአርዓያነት የሚጠቀስ መሆኑን አንስተዋል፡፡
በዚህም የኢትዮጵያ መንግሥት ለትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር መተግበር ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት እየተሰሩ ባሉ ሥራዎች ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታዋ የአለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ ምክትል ኃላፊ ሙቲንታ ሀምባይን (ዶ/ር) በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ሁለቱ አካላት በቀጣይ የኢትዮጵያ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብርን ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል።
በዚሁ ጊዜ ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ የኢትዮጵያ መንግሥት ለትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ለመርሃ-ግብሩ የሚመድቡት በጀት አየጨመረ መምጣቱንና ህብረተሰቡም ለመርሃ-ግብሩ ውጤታማነት የሚያደርገው ተሳትፎ በየጊዜው እያደገ የመጣ መሆኑን አንስተዋል፡፡
የአለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ሙቲንታ በበኩላቸው የኢትዮጵያ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር በአፍሪካ ትልቁና ቀዳሚ መሆኑን ጠቅሰው በቅርቡ በተካሄደው አለም አቀፍ የትምህርት ቤት ምገባ ጥምረት ስብሰባ ላይ እውቅና የተሰጠውና በአርዓያነት የሚጠቀስ መሆኑን አንስተዋል፡፡
በዚህም የኢትዮጵያ መንግሥት ለትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር መተግበር ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት እየተሰሩ ባሉ ሥራዎች ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል፡፡
Oct 17, 2025
68
የትምህርት ሚንስትሩ የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲን በጋምቤላ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተመደቡ ተማሪዎችን በጊዜያዊነት ለመቀበል እያደረገ ያለውን ቅድመ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር እያስገነባቸው ባሉ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለማስተማር ከመላ ሀገሪቱ አወዳድሮ የተቀበላቸውና በጋምቤላ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት የተመደቡ ተማሪዎች በጊዜያዊነት በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ለማስተማር የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛል።
በዚህም ዩኒቨርሲቲው ለእነዚህ ተማሪዎች የመማር ማስተማር አገልግሎት ያዘጋጃቸውን የተማሪዎች ቤተ-መጽሐፍት፣ የኮምፒውተር ክፍል፣ የመመገቢያ አዳራሽ፣ እና የመኝታ ክፍሎች እና ሌሎችንም አይተዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ሚንስትሩ በዩኒቨርሲቲው የሚገኙትን ስማርት እና ኮንፈረንስ ክፍሎች እንዲሁም የኬሚስትሪና የማይክሮ ባዮሎጂ ቤተ-ሙከራዎችን የጎበኙ ሲሆን በዩኒቨርሲቲው ጥሩ መሻሻሎች መኖራቸውን ገልጸዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርታቸው የላቁና ብቁ ተወዳሪ እንዲሁም ወደፊት የሀገር መሪ የሚሆኑ ልጆችን ለማፍራት ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እያስገነባ ሲሆን በአምስቱ በቅርቡ የመማር ማስተማር ሥራ የሚጀመር ይሆናል።
የትምህርት ሚንስትሩ የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲን በጋምቤላ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተመደቡ ተማሪዎችን በጊዜያዊነት ለመቀበል እያደረገ ያለውን ቅድመ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር እያስገነባቸው ባሉ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለማስተማር ከመላ ሀገሪቱ አወዳድሮ የተቀበላቸውና በጋምቤላ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት የተመደቡ ተማሪዎች በጊዜያዊነት በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ለማስተማር የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛል።
በዚህም ዩኒቨርሲቲው ለእነዚህ ተማሪዎች የመማር ማስተማር አገልግሎት ያዘጋጃቸውን የተማሪዎች ቤተ-መጽሐፍት፣ የኮምፒውተር ክፍል፣ የመመገቢያ አዳራሽ፣ እና የመኝታ ክፍሎች እና ሌሎችንም አይተዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ሚንስትሩ በዩኒቨርሲቲው የሚገኙትን ስማርት እና ኮንፈረንስ ክፍሎች እንዲሁም የኬሚስትሪና የማይክሮ ባዮሎጂ ቤተ-ሙከራዎችን የጎበኙ ሲሆን በዩኒቨርሲቲው ጥሩ መሻሻሎች መኖራቸውን ገልጸዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርታቸው የላቁና ብቁ ተወዳሪ እንዲሁም ወደፊት የሀገር መሪ የሚሆኑ ልጆችን ለማፍራት ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እያስገነባ ሲሆን በአምስቱ በቅርቡ የመማር ማስተማር ሥራ የሚጀመር ይሆናል።
Oct 17, 2025
64
የትምህርት ሚኒስትሩ በጋምቤላ ክልል እየተገነባ የሚገኘውን ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የደረሰበት ደረጃ ተመለከቱ።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በትምህርት ሚኒስቴር ድጋፍ በጋምቤላ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የግንባታ ሂደት የደረሰበትን ደረጃ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በምልከታቸው ወቅት እንዳሉት የሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱ ግንባታው ከተጀመረ አጭር ጊዜ ቢሆንም የደረሰበት ደረጃ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸው በዚሁ ፍጥነት ጥራቱን የጠበቀና ለተማሪዎች አመቺ ተደርጎ ሊገነባ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ሁሉም በሀገራችን የሚኖሩ ልጆች በተቻለ መጠን ተመጣጣኝ ትምህርት፣ እውቀትና ክህሎት ማግኘት አለባቸው ያሉት ሚኒስትሩ ለዚህም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ በበኩላቸው የሞደል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታው ከታሰበው በላይ በፍጥነት እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመው በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅም ስራው ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተናግረዋል።
ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱን እየገነባ የሚገኘው ናይል ሌችዌ ኮንስትራክሽን እና ውሃ ስራዎች ድርጅት የፕሮጀክቱ ግንባታ 42.1% እንደደረሰ ለከፍተኛ አመራሮቹ ገለጻ አድርገዋል።
በቀጣይም የፕሮጀክቱ ግንባታ በጥራትና በፍጥነት በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ በትጋት እየተሰራ እንደሚገኝ የፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ቦም ኮት ገልጸዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርትን በፍትሃዊነት ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች 31 የሚደርሱ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን እያስገናባ ይገኛል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በትምህርት ሚኒስቴር ድጋፍ በጋምቤላ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የግንባታ ሂደት የደረሰበትን ደረጃ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በምልከታቸው ወቅት እንዳሉት የሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱ ግንባታው ከተጀመረ አጭር ጊዜ ቢሆንም የደረሰበት ደረጃ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸው በዚሁ ፍጥነት ጥራቱን የጠበቀና ለተማሪዎች አመቺ ተደርጎ ሊገነባ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ሁሉም በሀገራችን የሚኖሩ ልጆች በተቻለ መጠን ተመጣጣኝ ትምህርት፣ እውቀትና ክህሎት ማግኘት አለባቸው ያሉት ሚኒስትሩ ለዚህም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ በበኩላቸው የሞደል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታው ከታሰበው በላይ በፍጥነት እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመው በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅም ስራው ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተናግረዋል።
ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱን እየገነባ የሚገኘው ናይል ሌችዌ ኮንስትራክሽን እና ውሃ ስራዎች ድርጅት የፕሮጀክቱ ግንባታ 42.1% እንደደረሰ ለከፍተኛ አመራሮቹ ገለጻ አድርገዋል።
በቀጣይም የፕሮጀክቱ ግንባታ በጥራትና በፍጥነት በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ በትጋት እየተሰራ እንደሚገኝ የፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ቦም ኮት ገልጸዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርትን በፍትሃዊነት ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች 31 የሚደርሱ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን እያስገናባ ይገኛል።
Oct 17, 2025
81
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ አዲስ ከተሾሙት የሀንጋሪ አምባሳደር ጋር ተወያዩ።
የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙትን የሀንጋሪ አምባሳደር አቲላ ቶዝን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል ።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ እና ሀንጋሪ በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር ሲሰሩ መቆየታቸውን አንስተዋል።
በተለይም በ2023 በትምህርት ሚኒስቴርና በሀንጋሪ ኢምባሲ በኩል የተፈረመውን የነጻ የትምህርት እድል ስምምነት በተመለከተ እስካሁን የተከናወኑ ተግባራት አንስተው ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ ክቡር ሚኒስትሩ ይህንን የጋራ መግባቢያ ስምምነት ሰነድ አስተካክሎ ለሀገራችን ልማትና ኢኮኖሚያዊ እድገት ጠቃሚ በሆኑ የትኩረት መስኮች በተለይም በፔትሮ ኬሚካል፣ በኒውክለር ሳይንስ፣ በማዕድን ልማት ፣ በቱሪዝምና ባህል እንዲሁም በሀገራችን በማይሰጡ የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ የነጻ የትምህርት እድል መስጠት በሚያስችል መልኩ ማሻሻልና መፈራረም እንደሚገባ ለአዲሱ አምባሳደር አብራርተውላቸዋል።
በኢትዮጵያ አዲሱ የሀንጋሪ አምባሳደር አቲላ አቶዝ በበኩላቸው ሚኒስትሩ ባቀረቡላቸው የሀገራችንን ልማትና ኢኮኖሚን በሚደግፉ አዳዲስ የትምህርት መስኮች ላይ ትብብር ለማድርግ በመሰረተ ሀሳብ ደረጃ ስምምነታቸውን ገልጽዋል።
በዚህም በሁለቱ ሀገራት መካከል የተጀመረውን የመግባቢያ ስምምነት ለማሻሻል ከሀገራቸው የሥራ ኃልፊዎች ጋር በመነጋገር እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
ሁለቱ አካላት በውይይታቸውም ከዚህ በፊት የነበረውን የመግባቢያ ስምምነት ለማሻሻልና በተለያዩ አዳዲስ የትምህርት መስኮች የነጻ የትምህርት እድል ለማመቻቸት ከስምምነት ላይ ደረሰዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙትን የሀንጋሪ አምባሳደር አቲላ ቶዝን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል ።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ እና ሀንጋሪ በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር ሲሰሩ መቆየታቸውን አንስተዋል።
በተለይም በ2023 በትምህርት ሚኒስቴርና በሀንጋሪ ኢምባሲ በኩል የተፈረመውን የነጻ የትምህርት እድል ስምምነት በተመለከተ እስካሁን የተከናወኑ ተግባራት አንስተው ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ ክቡር ሚኒስትሩ ይህንን የጋራ መግባቢያ ስምምነት ሰነድ አስተካክሎ ለሀገራችን ልማትና ኢኮኖሚያዊ እድገት ጠቃሚ በሆኑ የትኩረት መስኮች በተለይም በፔትሮ ኬሚካል፣ በኒውክለር ሳይንስ፣ በማዕድን ልማት ፣ በቱሪዝምና ባህል እንዲሁም በሀገራችን በማይሰጡ የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ የነጻ የትምህርት እድል መስጠት በሚያስችል መልኩ ማሻሻልና መፈራረም እንደሚገባ ለአዲሱ አምባሳደር አብራርተውላቸዋል።
በኢትዮጵያ አዲሱ የሀንጋሪ አምባሳደር አቲላ አቶዝ በበኩላቸው ሚኒስትሩ ባቀረቡላቸው የሀገራችንን ልማትና ኢኮኖሚን በሚደግፉ አዳዲስ የትምህርት መስኮች ላይ ትብብር ለማድርግ በመሰረተ ሀሳብ ደረጃ ስምምነታቸውን ገልጽዋል።
በዚህም በሁለቱ ሀገራት መካከል የተጀመረውን የመግባቢያ ስምምነት ለማሻሻል ከሀገራቸው የሥራ ኃልፊዎች ጋር በመነጋገር እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
ሁለቱ አካላት በውይይታቸውም ከዚህ በፊት የነበረውን የመግባቢያ ስምምነት ለማሻሻልና በተለያዩ አዳዲስ የትምህርት መስኮች የነጻ የትምህርት እድል ለማመቻቸት ከስምምነት ላይ ደረሰዋል።
Oct 16, 2025
92